የማኅበሩ ተልዕኮ

የኢትዮጵያውያን ኮሚኒቲ በቀጠር  የተመሰረተው በቀጠር ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ማህበራዊ ድጋፍና አገልግሎቶችን ለማቅረብ ነው። የኮሚኒቲ ማኅበሩ ኢትዮጵያውያንን በማኀበሩ ስር በማሰባሰብ መብታቸውንና ጥቅማቸውን ስለሚከበርበት ሁኔታ እንዲወያዩ፣ እርስ በርስ እንዲደጋገፉ፣ ስለአገራቸው ሁኔታ ወቅታዊ መረጃ እንዲያገኙ፣ ማንነታቸውን የሚገልጹ፣ ማኀበራዊና ባህላዊ እሴቶቻቸውን የሚያከብሩና ለሌሎች የሚያስተዋውቁ ዝግጅቶችን እንዲታደሙ፣ እንዲሁም በአገራቸው በሚከናወኑ የልማት እንቅስቃሴዎች በየአቅማቸው ተሳታፊ እንዲሆኑ ይሰራል።

የኛ ቡድን

ተደጋግመው የሚነሱ ጥያቄዎች

ኮሚኒት ማህበሩ ችግር ለደረሰባቸው ዜጎቻችን ከህግና መብት ጋር ተያያዥ ምክር በመስጠት፣ የማስታረቅ ስራ በመስራት፣ በሆስፒታል ወይም CID በመጎብኘት፣ በመጠለያ በማቆየት፣ ወዘተ ይደግፋል። 
የማህበሩ ዋና የገቢ ምንጭ ከአባላት የሚሰበሰብ ዓመታዊ የአባልነት ክፍያ ነው። ከዚህ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ኤምባሲ አገልግሎት ለማግኘት ለመጡ ደንበኞች ተጓዳኝ አገልግሎትችን በማቅርብ (ለምሳሌ ፎርም በመሙላት፣ ፎት በማንሳት፣ ወዘተ) ገቢ ያገኛል።
የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ የሚገኘውን ጽህፈት ቤታችንን በመጎብኘት በአባልነት መመዝገብ ይችላሉ።
በኤምባሲው የሚገኘው በጽህፈት ቤታችን በአካለ በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 3006 4604 በመደወል ድጋፍ መጠየቅ ይቻላል። ለአስቸኳይ ጉዳዮች፣ የዜጎች ጉዳይ መኮንናችንን በስልክ ቁጥር 7725 9900 ማግኘት ይቻላል።
ዋንኛው ዝግጅታችን በየዓመቱ የሚከበረው የኢትዮጵያ ቀን በዓል ነው። ይህ በዓል በተለምዶ የእግር ኳስ ውድድር፣ የሙዚቃ ኮንሰርትና ሌሎች ማህበረሰቡን አሳታፊ የሆኑ ፕሮግራሞችን ያካተተ ነው። ከዚህ በተጨማሪ የቀጠር ብሔራዊ ቀን፣ ብሔራዊ የስፖርት ቀን፣ የዳይመንድ ሊግ አትሌቲክስ ውድድር ለመሳሰሉ ዝግጅቶች ማህብረሰቡን የማነቃቃትና የማሳተፍ ስራ ይሰራል።
ስለዝግጅቶቻችን በዚሁ ድረ ገጻችንና በፌስቡክ ገጻችን መረጃ እናቀርባለን። 
ይህንን የመመዝገቢያ ቅጽ በመሙላት የራስዎንና የድርጅትዎን መረጃ አጋሩን። ለተጨማሪ ድጋፍ ወደ ጽህፈት ቤታችን መምጣት ወይም መደወል ይችላሉ።